bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
/
Job 18
Job 18
Amharic NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
1
ሹሐዊው በልዳዶስ እንዲህ ሲል መለሰ፤
2
“ይህን ንግግር የምትጨርሰው መቼ ነው? እስኪ ልብ ግዛ፤ ከዚያ በኋላ እንነጋገራለን።
3
ለምን እንደ ከብት መንጋ እንቈጠራለን? እንደ ደንቈሮስ ለምን ታየናለህ?
4
አንተ በቍጣ የነደድህ እንደ ሆነ፣ ምድር ባዶዋን ትቀራለች? ወይስ ዐለት ከስፍራው ተነቅሎ ይወሰዳል?
5
“የክፉዎች መብራት ይጠፋል፤ የእሳቱም ነበልባል ድርግም ይላል።
6
የድንኳኑ ብርሃን ይጨልማል፤ መብራቱም በላዩ ይጠፋል፤
7
የርምጃው ብርታት ይደክማል፤ የገዛ ዕቅዱም ይጥለዋል።
8
እግሩ በወጥመድ ይያዛል፤ በመረብም ይተበተባል።
9
አሽክላ ተረከዙን ይይዘዋል፤ ወስፈንጥርም ያጣብቀዋል።
10
በምድር ላይ የሸንበቆ ገመድ፣ በመንገዱም ላይ ወጥመድ በስውር ይቀመጥለታል።
11
ድንጋጤ በዙሪያው ያስፈራራዋል፤ ተከትሎም ያሳድደዋል።
12
መቅሠፍት ሊውጠው ቀርቧል፤ ጥፋትም የእርሱን ውድቀት ይጠባበቃል።
13
ደዌ ቈዳውን ይበላል፤ የሞት በኵርም ቅልጥሙን ይውጣል።
14
ተማምኖ ከሚኖርበት ድንኳን ይነቀላል፤ ወደ ድንጋጤም ንጉሥ ይነዳል።
15
ድንኳኑ በእሳት ይያያዛል፤ በመኖሪያውም ላይ ዲን ይበተናል።
16
ሥሩ ከታች ይደርቃል፤ ቅርንጫፉም ከላይ ይረግፋል።
17
መታሰቢያው ከምድር ገጽ ይጠፋል፤ ስሙም በአገር አይነሣም።
18
ከብርሃን ወደ ጨለማ ይጣላል፤ ከዓለምም ይወገዳል።
19
በሕዝቡ መካከል ልጅ ወይም ዘር አይኖረውም፤ በኖረበትም አገር ተተኪ አያገኝም።
20
ባጋጠመው ሁኔታ የምዕራብ ሰዎች ይደነግጣሉ፤ የምሥራቅም ሰዎች በፍርሀት ይዋጣሉ።
21
በርግጥ የክፉ ሰው መኖሪያ፣ እግዚአብሔርንም የማያውቅ ሰው መድረሻ ይህ ነው።”
← Chapter 17
Chapter 19 →