bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
/
Job 29
Job 29
Amharic NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
1
ኢዮብም እንዲህ ሲል ንግግሩን ቀጠለ፤
2
“በእግዚአብሔር የተጠበቅሁበትን ዘመን፣ ያለፈውንም ወራት ምንኛ ተመኘሁ!
3
ያን ጊዜ መብራቱ በራሴ ላይ ይበራ ነበር፤ በብርሃኑም በጨለማ ውስጥ ዐልፌ እሄድ ነበር፤
4
እኔም ብርቱ ነበርሁ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅነት ቤቴን ይባርክ ነበር፤
5
ሁሉን የሚችል አምላክ ከእኔ ጋር ነበረ፤ ልጆቼም በዙሪያዬ ነበሩ፤
6
መንገዴ በቅቤ የራሰ ነበር፤ ዐለቱም የወይራ ዘይት ያመነጭልኝ ነበር።
7
“ወደ ከተማዪቱ በር ብቅ ባልሁ ጊዜ፣ በአደባባይዋም በወንበር በተቀመጥሁ ጊዜ፣
8
ጐበዛዝት አይተውኝ ገለል ይሉ፣ ሽማግሌዎችም ተነሥተው ይቆሙ ነበር።
9
የሰፈሩ ታላላቅ ሰዎች ከመናገር ይቈጠቡ፣ እጃቸውንም በአፋቸው ላይ ይጭኑ ነበር፤
10
የመኳንንት ድምፅ ጸጥ ይል፣ ምላሳቸውም ከላንቃቸው ጋር ይጣበቅ ነበር፤
11
የሰሙኝ ሁሉ ያሞጋግሱኝ፣ ያዩኝም ያመሰግኑኝ ነበር፤
12
ለርዳታ የሚጮኸውን ችግረኛ፣ ድኻ ዐደጉንም ታድጌአለሁና።
13
በሞት አፋፍ ላይ የነበረ መርቆኛል፤ የመበለቲቱንም ልብ አሳርፌአለሁ።
14
ጽድቅን እንደ ልብስ ለበስሁ፤ ፍትሕም መጐናጸፊያዬና ጥምጥሜ ነበር።
15
ለዕውራን ዐይን፣ ለዐንካሶችም እግር ነበርሁ።
16
ለችግረኛው አባት፣ ለባይተዋሩ ተሟጋች ነበርሁ።
17
የኀጢአተኛውን ክራንቻ ሰበርሁ፤ የነጠቀውንም ከጥርሶቹ አስጣልሁ።
18
“እኔም በልቤ እንዲህ አልሁ፤ ‘ዘመኔ እንደ አሸዋ በዝቶ፣ በቤቴ ተደላድዬ እሞታለሁ፤
19
ሥሬ ወደ ውሃ ይዘረጋል፤ ጠልም በቅርንጫፌ ላይ ያድራል፤
20
ክብሬ በውስጤ አዲስ እንደ ሆነ፣ ቀስትም በእጄ እንደ በረታ ይኖራል።’
21
“ሰዎች ምክሬን በጸጥታ በመጠባበቅ፣ በጕጕት አደመጡኝ።
22
እኔ ከተናገርሁ በኋላ፣ የሚናገር ሰው አልነበረም፤ ቃሌም እየተንጠባጠበ በጆሯቸው ይገባ ነበር።
23
ዝናብ እንደሚጠብቅ ሰው ጠበቁኝ፤ ቃሌንም እንደ በልግ ዝናብ ጠጡ፤
24
በሣቅሁላቸው ጊዜ እውነት አልመሰላቸውም፤ የፊቴም ብርሃን ብርቃቸው ነበር።
25
መንገድ መርጬላቸው አለቃቸው ሆኜ ተቀመጥሁ፤ በሰራዊትም መካከል እንዳለ ንጉሥ ኖርሁ፤ ሐዘንተኞችንም እንደሚያጽናና ነበርሁ።
← Chapter 28
Chapter 30 →