bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic Catholic Version (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)) No Year
/
Psalms 98
Psalms 98
Amharic Catholic Version (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)) No Year
1
የዳዊት መዝሙር። ለጌታ አዲስ መዝሙር ዘምሩ፥ ድንቅ ነገሮችን አድርጎአልና፥ ቀኙ፥ የተቀደሰ ክንዱም ለእርሱ ማዳን አደረገ።
2
ጌታ ማዳኑን አስታወቀ፥ በአሕዛብም ፊት ጽድቁን ገለጠ።
3
ለእስራኤል ቤት ያለውን ጽኑ ፍቅርና ታማኝነት አስታወሰ፥ የምድር ዳርቻዎች ሁሉ የአምላካችንን ማዳን አዩ።
4
ምድር ሁሉ ሆይ፥ ለጌታ እልል በሉ፥ በደስታ ፈንድቁ፥ ዘምሩም።
5
ለጌታ በመሰንቆ፥ በመሰንቆና በዝማሬ ድምፅ ዘምሩ።
6
በዋሽንትና በመለከት ድምፅ በንጉሡ በጌታ ፊት እልል በሉ።
7
ባሕርና ሞላዋ፥ ዓለምም በእርሷም የሚኖሩ ይናወጡ።
8
ወንዞችም በአንድነት በእጅ ያጨብጭቡ፥ ተራሮችም በደስታ ይዘምሩ፥ በምድር ሊፈርድ ይመጣልና።
9
ዓለምንም በጽድቅ አሕዛብንም በቅንነት ይፈርዳል።
← Chapter 97
Chapter 99 →