bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic Catholic Version (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)) No Year
/
Job 23
Job 23
Amharic Catholic Version (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)) No Year
1
ኢዮብም መለሰ፤ እንዲህም አለ፦
2
“ዛሬም ደግሞ የኀዘን እንጉርጉሮዬ ገና መራራ ነው፥ በመቃተት ብጮኽም እጁ በእኔ ላይ እንደ ከበደች ናት።
3
እርሱን እንዴት እንደማገኘው ምነው ባወቅሁ! ወደ ተቀመጠበትስ ስፍራ ምነው በደረስሁ!
4
በፊቱ አቤቱታዬን አቀርብ ነበር፥ አፌንም በማስረጃ እሞላው ነበር።
5
የሚመልስልኝም ቃል ምን እንደሆነ አውቅ ነበር፥ የሚለኝንም አስተውል ነበር።
6
በታላቅ ኃይሉ ከእኔ ጋር ይምዋገት ነበርን? ይልቁንም! ማዳመጥ ይበቃው ነበር።
7
የሚከራከረው ቅን ሰው መሆኑን ይመሰክር ነበር፥ እኔም በፈራጅ ፊት ለዘለዓለም ነፃ እወጣ ነበር።”
8
“እነሆ፥ ወደፊትም ብሄድ፥ እርሱ የለም፥ ወደ ኋላም ብሄድ፥ አላየውም፥
9
ወደሚሠራበት ወደ ግራ ብሄድ አይታየኝም፥ በቀኜም ይሰወራል፥ አላየውምም፥
10
የምሄድበትን መንገድ ያውቃል፥ ከፈተነኝም በኋላ እንደ ወርቅ እወጣለሁ።
11
እግሬ ዱካውን ተከትሎአል፥ መንገዱንም ጠብቄአለሁ፥ ከመስመር አልወጣሁም።
12
ከተናገራቸው ትእዛዛት አልኮበለልኩም፥ የአፉን ቃል በልቤ ደብቄአለሁ።
13
እርሱ ግን የሚተካከለው የለውም፥ ማንስ ውሳኔውን ያስቀይረዋል? የወደደውንም ያደርጋል።
14
በእኔ ላይ የወሰነውን ይፈጽማል፥ እንደዚህ ያሉ ብዙ ብያኔዎች እንዳሉት።
15
ስለዚህ በፊቱ ደነገጥሁ፥ ባሰብሁም መጠን ፈራሁት።
16
እግዚአብሔር ልቤን አባብቶታልና፥ ሁሉንም የሚችል አምላክ አስደንግጦኛል።
17
በጨለማው አልተደመሰስኩም፥ ነገር ግን ድቅድቁ ጨለማ ፊቴን ሸፈነ።”
← Chapter 22
Chapter 24 →