bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
/
Psalms 59
Psalms 59
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
1
አቤቱ፥ ጣልኸን አፈረስኸንም፤ ገረፍኸን፥ ይቅርም አልኸን።
2
ምድርን አናወጥሃት፥ አወክሃትም፤ ተናውጣለችና ቍስልዋን ፈወስኻት።
3
ለሕዝብህ ጭንቅን አሳየሃቸው፥ አስደንጋጩንም ወይን አጠጣኸን።
4
ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው፥ ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ።
5
ወዳጆችህም፥ እንዲድኑ በቀኝህ አድን፥ ስማኝም።
6
እግዚአብሔር በመቅደሱ ተናገረ፤ ደስ ይለኛል፥ ምርኮንም እካፈላለሁ፥ የሸለቆ ቦታዎችን እሰፍራለሁ።
7
ገለዓድ የእኔ ነው፥ ምናሴም የእኔ ነው፤ ኤፍሬም የራሴ መጠጊያ ነው። ይሁዳ ንጉሤ ነው፤
8
ካህን ሞአብም ተስፋዬ ነው በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እዘረጋለሁ፤ ፍልስጥኤምም ይገዙልኛል።
9
ቅጥር ወደ አለባት ወደ ጽኑ ከተማ ማን ይወስደኛል? ማንስ እስከ ኤዶምያስ ይመራኛል?
10
አቤቱ፥ የጣልኸን አንተ አይደለህምን? አምላካችን ሆይ፥ ከሠራዊታችን ጋር አትወጣም።
11
በመከራችን ረድኤትን ስጠን፥ በሰውም መታመን ከንቱ ነው።
12
በእግዚአብሔር ኀይልን እናደርጋለን፤ እርሱም የሚያስጨንቁንን ያዋርዳቸዋል።
← Chapter 58
Chapter 60 →