bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
/
Psalms 19
Psalms 19
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
1
በመከራህ ቀን እግዚአብሔር ይስማህ፤ የያዕቆብ አምላክ ስምም ይቁምልህ።
2
ከመቅደሱ ረድኤትን ይላክልህ፥ ከጽዮንም ይቀበልህ።
3
መሥዋዕትህን ያስብልህ፤ ቍርባንህንም ያለምልምልህ።
4
እግዚአብሔር እንደ ልብህ ይስጥህ ፈቃድህንም ሁሉ ይፈጽምልህ።
5
በማዳንህ ደስ ይለናል፤ በእግዚአብሔር በአምላካችን ስም ከፍ ከፍ እንላለን፤ ልመናህን ሁሉ እግዚአብሔር ይፈጽምልህ።
6
እግዚአብሔር የቀባውን እንዳዳነው ዛሬ ዐወቅሁ፤ ከሰማይ መቅደሱ ይመልስለታል በቀኙ የማዳን ኀይል።
7
እነዚያ በፈረሶችና በሰረገላዎች ይታመናሉ፤ እኛ ግን በአምላካችን በእግዚአብሔር ስም ከፍ ከፍ እንላለን።
8
እነርሱ ተሰነካክለው ወደቁ፤ እኛ ግን ተነሣን፥ ጸንተንም ቆምን።
9
አቤቱ፥ ንጉሥን አድነው፥ በምንጠራህም ቀን ስማን።
← Chapter 18
Chapter 20 →