bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
/
Psalms 145
Psalms 145
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
1
ነፍሴ እግዚአብሔርን ታመሰግነዋለች።
2
በሕይወቴ ሳለሁ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ፤ በምኖርበት ዘመን መጠን ለአምላኬ እዘምራለሁ።
3
ማዳን በማይችሉ በአለቆችና በሰው ልጆች አትታመኑ።
4
ነፍሳቸው ትወጣለች፥ ወደ መሬትም ይመለሳሉ፤ ያንጊዜ ምክራቸው ሁሉ ይጠፋል።
5
የያዕቆብ አምላክ ረዳቱ የሆነ፥ መታመኛውም በአምላኩ በእግዚአብሔር የሆነ ሰው ብፁዕ ነው።
6
እርሱም ሰማይንና ምድርን ባሕርንም፥ በእነርሱ ውስጥ ያለውንም ሁሉ የፈጠረ፤ እውነትን ለዘለዓለም የሚጠብቅ፤
7
ለተበደሉትም የሚፈርድላቸው፥ ለተራቡ ምግብን የሚሰጥ ነው። እግዚአብሔር የታሰሩትን ይፈታቸዋል፤
8
እግዚአብሔር የወደቁትን ያነሣቸዋል፤ እግዚአብሔር ዕውሮችን ጥበበኞች ያደርጋቸዋል፤ እግዚአብሔር ጻድቃንን ይወድዳቸዋል፤
9
እግዚአብሔር ስደተኞችን ይጠብቃቸዋል፤ ድሃ አደጎችንና ባልቴቶችን ይቀበላቸዋል፤ የኃጥኣንንም መንገድ ያጠፋል።
10
እግዚአብሔር ለዘለዓለም ይነግሣል፤ ጽዮን ሆይ፥ አምላክሽ ለልጅ ልጅ ነው።
← Chapter 144
Chapter 146 →