bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
/
Psalms 140
Psalms 140
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
1
አቤቱ፥ ወደ አንተ ጮኽሁ፤ ስማኝ፤ ወደ አንተ ስጮኽም የልመናዬን ቃል አድምጥ።
2
ጸሎቴን በፊትህ እንደ ዕጣን ተቀበልልኝ፥ እጆቼ የሠርክ መሥዋዕትን አነሡ።
3
አቤቱ፥ ለአፌ ጠባቂ፥ ለከንፈሮቼም ጽኑዕ መዝጊያን አኑር።
4
ልቤን ወደ ክፉ ነገር አትመልሰው፥ ዐመፃን ከሚያደርጉ ሰዎች ጋር ለኀጢአት ምክንያት እንዳልሰጥ፤ ከምርጦቻቸውም ጋር አልተባበር።
5
በጽድቅ ገሥጸኝ፥ በምሕረትም ዝለፈኝ፥ የኀጢአተኛ ዘይትን ግን ራሴን አልቀባም፤ ዳግመኛም ጸሎቴ ይቅር እንዳትላቸው ነውና።
6
ኀያላኖቻቸው በዓለት አጠገብ ተጣሉ፥ ተችሎኛልና ቃሌን ስሙኝ።
7
እንደ ጓል በምድር ላይ ተሰነጣጠቁ እንዲሁ አጥንቶቻቸው በሲኦል ተበተኑ፥
8
አቤቱ፥ ጌታዬ፥ ዐይኖቼ ወደ አንተ ናቸውና፤ በአንተ ታመንሁ፥ ነፍሴን አታውጣት።
9
ከሰወሩብኝ ወጥመድ፥ ዐመፃንም ከሚያደርጉ ሰዎች እንቅፋት ጠብቀኝ።
10
እኔ ብቻዬን እስካልፍ ድረስ ኃጥኣን በወጥመዳቸው ይውደቁ።
← Chapter 139
Chapter 141 →