bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
/
Job 26
Job 26
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
1
ኢዮብም መለሰ፥ እንዲህም አለ፦
2
“ማንን ትደግፋለህ? ማንንስ ልትረዳ ትወድዳለህ? ጥንቱን ኀይሉ ብዙ፥ ክንዱም ጽኑ የሆነ እርሱ አይደለምን?
3
ለማንስ ታማክራለህ? ጥበብ ሁሉ ለእርሱ አይደለምን? ማንንስ ትከተላለህ? ታላቅ ኀይል ያለው እርሱ አይደለምን?
4
ነገርን ለማን ትናገራለህ? የማንስ መንፈስ ከአንተ ዘንድ ይወጣል?
5
ኀያላን ከውኆች በታች፥ በውኆችም ውስጥ ከሚኖሩ ይወለዳሉን?
6
ሲኦል በፊቱ ራቁቱን ነው፥ ሞትንም ከእርሱ የሚጋርደው የለም።
7
ሰማይን በባዶ ስፍራ ላይ ይዘረጋል፥ ምድሪቱንም አንዳች አልባ ያንጠለጥላል።
8
ውኃውን በደመና ውስጥ ይቋጥራል፥ ደመናውም ከታች አይቀደድም።
9
የዙፋኑን ፊት ይከድናል፥ ደመናውንም ይዘረጋበታል።
10
ብርሃን ከጨለማ እስከሚለይበት ዳርቻ ድረስ፥ የውኃውን ፊት በተወሰነ ትእዛዙ ከበበው።
11
የሰማይ አዕማድ ይንቀጠቀጣሉ፥ ከተግሣጹም የተነሣ ይደነግጣሉ።
12
በኀይሉ ባሕርን ጸጥ ያደርጋል፥ በማስተዋሉም ዐንበሪውን ይገለብጠዋል።
13
የሲኦል በረኞች ለእርሱ አደሉ። በትእዛዙም ዐመፀኛውን እባብ ገደለው።
14
እነሆ ይህ የመንገዱ ክፍል ነው፤ የቀሩትንም ነገሮቹን እንሰማለን፤ በሚያደርግበትስ ጊዜ የነጐድጓዱን ኀይል የሚያውቅ ማን ነው?”
← Chapter 25
Chapter 27 →