bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic New Standard Translation (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም) 2005
/
Numbers 34
Numbers 34
Amharic New Standard Translation (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም) 2005
1
እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ አለው፤
2
“እስራኤላውያንን እንዲህ ብለህ እዘዝ፦ እኔ ወደምሰጣችሁ ወደ ከነዓን ምድር በምትገቡበት ጊዜ የርስታችሁ ወሰን እንደሚከተለው ይሆናል፦
3
የደቡብ ድንበር ከጺን ምድረ በዳ ተነሥቶ የኤዶምን ጠረፍ እያዋሰነ ያልፋል፤ ይኸውም በስተ ምሥራቅ በኩል የሚጀምረው ከሙት ባሕር በስተ ደቡብ ጫፍ ላይ ነው።
4
ከዚያም ወደ ዐቅራቢም መተላለፊያ ወደ ደቡብ በማምራት በጺን አልፎ እስከ ቃዴስ በርኔ ይደርሳል፤ ከዚያም በሐጻርአዳር ሰሜናዊ ምዕራብ አልፎ እስከ ዓጽሞን ይደርሳል።
5
ከዓጽሞን ተነሥቶ የግብጽን ሸለቆ በመዞር በሜዲትራኒያን ባሕር ይቆማል።
6
“የምዕራቡ ወሰን የሜድትራኒያን ባሕር ጠረፍ ይሆናል።
7
“የሰሜኑ ወሰን የሜዲቴራኒያንን ባሕር በመከተል እስከ ሖር ተራራ ይሆናል፤
8
ከሖርም ተራራ ወደ ሐማት መግቢያ ምልክት ይደርሳል፤ የድንበሩም መጨረሻ ጸዳድ ይሆናል።
9
ወደ ዚፍሮን ከተሻገረም በኋላ በሐጻርዔናን ይቆማል፤ ይህም የሰሜን ድንበራችሁ ይሆናል።
10
“የምሥራቁ ወሰናችሁን ከሐጻርዔናን እስከ ሸፋም ምልክት ታደርጋላችሁ
11
ወሰኑም ከሴፋም ተነሥቶ ከዓይን በስተምሥራቅ በኩል ወደ ሪብላ ይቀጥልና በገሊላ ባሕር በስተ ምሥራቅ ወዳሉት ኮረብታዎች ይደርሳል።
12
ወሰኑም ወደ ዮርዳኖስ ይወርዳል፤ መጨረሻውም የሙት ባሕር ይሆናል። እነዚህም የምድራችሁ ዙሪያ አዋሳኞች ይሆናሉ።”
13
ሙሴ እስራኤላውያንን እንዲህ ብሎ አዘዛቸው፦ “ለዘጠኝ ተኩል ነገዶች እንዲሰጥ እግዚአብሔር ያዘዘው በዕጣ የምትካፈሉት ርስት ይህ ነው።
14
የሮቤልና የጋድ ነገዶች፥ እንዲሁም የምናሴ ነገድ እኩሌታ በየቤተሰባቸው በመከፋፈል፥
15
በዮርዳኖስ ማዶ ከኢያሪኮ በስተምሥራቅ፥ በፀሐይ መውጫ በኩል ርስታቸውን ተቀብለዋል።”
16
እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ አለው፤
17
“ካህኑ አልዓዛርና የነዌ ልጅ ኢያሱ ምድሪቱን በሕዝቡ መካከል ያከፋፍሉ፤
18
ምድሪቱን ለማከፋፈል ይረዱ ዘንድ ከየነገዱ አንድ አንድ መሪ ውሰድ።”
19
የሰዎቹም ስም ይህ ነው፤ ከይሁዳ ነገድ የይፉኔ ልጅ ካሌብ፥
20
ከስምዖን ነገድ የአሚሁድ ልጅ ሰላሚኤል፥
21
ከብንያም ነገድ የኪስሎን ልጅ ኤልዳድ፥
22
ከዳን ነገድ የዮግሊ ልጅ ቡቂ፥
23
ከዮሴፍ ልጆች፥ ከምናሴ ነገድ የሱፊድ ልጅ አኒኤል፥
24
ከኤፍሬም ነገድ የሺፍጣን ልጅ ቀሙኤል፥
25
ከዛብሎን ነገድ የፈርናክ ልጅ ኤሊሳፈን፥
26
ከይሳኮር ነገድ የሖዛ ልጅ ፖልቲኤል፥
27
ከአሴር ነገድ የሴሌሚ ልጅ አሒሁድ፥
28
ከንፍታሌም ነገድ የአሚሁድ ልጅ ፔዳሄል፥
29
እንግዲህ ለእስራኤል ሕዝብ በከነዓን ምድር ርስት እንዲያካፍሉ እግዚአብሔር የመረጣቸው ሰዎች እነዚህ ናቸው።
← Chapter 33
Chapter 35 →