bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
/
Job 23
Job 23
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
1
ኢዮብም መለሰ፥ እንዲህም አለ፦
2
“ዛሬም ዘለፋዬ ከእጄ እንደ ሆነ ዐወቅሁ። እጁንም በእኔ ላይ አከበደ፥ አስለቀሰኝም።
3
እርሱን ወዴት እንደማገኘው ምነው ባወቅሁ! ወደ ነገሩ ፍጻሜም ምነው በደረስሁ!
4
የሠራሁት ቢኖር ይነግረኝ ነበረ፥ ስከራከርም አፌ ዝም አይልም ነበር።
5
የሚሰጠኝንም ፈውስ አውቅ ነበር፥ የሚለኝንም አስተውል ነበር።
6
በኀይሉ ብዛት ቢመጣብኝም እንኳ በቍጣው አያስፈራራኝም ነበር።
7
እውነትና ቅንነት ከእርሱ ዘንድ ናቸውና። ከፍርዴም ለዘለዓለም ያሳርፈኝ ነበር።
8
እነሆ፥ ወደ ፊት እሄዳለሁ፥ እንግዲህም አልኖርም፤ ስለ ፍጻሜውም አላውቅም፤
9
ወደሚሠራበትም ወደ ግራ ብሄድ አልመለከተውም፤ ቀኝ እጁ ይከብበኛል፤ ነገር ግን አላየውም።
10
መንገዴን ፈጽሞ ዐወቀ፥ እንደ ወርቅም ፈተነኝ
11
እንደ ትእዛዙ እወጣለሁ፥ መንገዱንም ጠብቄአለሁ፥ ፈቀቅም አላልሁም።
12
ከትእዛዙም አላለፍሁም፤ ቃሉን በልቤ ሰውሬአለሁ።
13
“ስለ ፍርድ የሚከራከር ማን ነው? እርሱ የወደደውን ያደርጋልና።
14
ስለዚህም እኔ ስለ እርሱ ቸኰልሁ፤ በተገሠጽሁም ጊዜ አሰብሁት።
15
ስለዚህ በፊቱ ደነገጥሁ፤ አስበዋለሁ፤ ከእርሱም የተነሣ እፈራለሁ።
16
እግዚአብሔር ግን ልቤን አቀለጠው፥ ሁሉን የሚችል አምላክም አስጨንቆኛል።
17
ጨለማም እንደሚመጣብኝ፥ ድቅድቁም ጨለማ ፊቴን እንደሚከድን አላወቅሁም።
← Chapter 22
Chapter 24 →